IEEC Seal

የዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስትያን መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ

International Ethiopian Evangelical Church Bible College

የሚለውጥ እውነት
የሚያገለግል ሕይወት

የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጃችን መምህራን በከፍተኛ የትምህርት ዝግጅታቸው ብቻ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ጥልቅ ፍቅር እና መንፈሳዊ ህይወት ያላቸው ናቸው። ተማሪዎችን በእውቀት ከመቅረጽ ባለፈ፣ በመንፈሳዊ እድገት እና በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር አርአያ በመሆን ያገለግላሉ። የወንጌል እውነትን በተግባር የሚኖሩ እና ለተማሪዎቻቸው ስኬት በቁርጠኝነት የሚሰሩ ታማኝ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው።

ሰርተፊኬት(Certificates)

በአንድ ዓመትጊዜ ውስጥ፣ ለክርስቲያናዊ ሕይወትዎና ለአገልግሎትዎ አስተማማኝ የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረትና እውቀት የሚጨብጡበት።

ተጨማሪ →

ዲፕሎማ (Diplomas)

በሁለት ዓመት የጥናት ቆይታ ለቤተክርስቲያን ተልዕኮና ለተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች ብቁ የሚያደርግ ልዩ የሰልጠና መርሃ-ግብር።

ተጨማሪ →

ዲግሪ (Degrees)

ጥልቅ የመለኮታዊ እውነት ምርምር ከተግባራዊ መንፈሳዊ አመራር ጋር የሚገናኝበት፣ ብቁና ባለራዕይ የእግዚአብሔር አገልጋዮችን የሚያፈራ

ተጨማሪ →

"የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ቅዱሱንም ማወቅ ማስተዋል ነው"

መጽሐፈ ምሳሌ 9:10

መሠረታችን በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ የጸና አገልግሎታችን ለዘመናችን ተገቢነት ያለው ፕሮግራሞችን ያካተተ ነው።

የዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስትያን መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ የመማሪያ መርሃ-ግብራችን ነፍስዎን ሲመግብ፣ አእምሮዎን ደግሞ ለማነቃቃት ተብሎ የተቀየሰ ነው።

ልምድ ያላቸው መምህራኖቻችን — ምሁራንና አገልጋዮች — በእያንዳንዱ እርምጃዎ ሊመሩዎት እዚህ ይገኛሉ።

በይበልጥ ለመረዳት ይጻፉልን
Library Study